የግርጌ ማስታወሻ
a ከተቃዋሚዎቹ መካከል አንዳንዶቹ “ነፃ የወጡ ሰዎች ምኩራብ” ተብሎ የሚጠራው ቡድን አባላት ነበሩ። እነዚህ ሰዎች በአንድ ወቅት በሮማውያን ተማርከው በኋላ ላይ ነፃ የወጡ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ፤ ወይም ደግሞ ወደ ይሁዲነት የተለወጡ ነፃ የወጡ ባሮች ይሆናሉ። እንደ ጠርሴሱ ሳኦል ሁሉ አንዳንዶቹ ከኪልቅያ የመጡ ነበሩ። ሳኦል፣ እስጢፋኖስን መቋቋም ካልቻሉት የኪልቅያ ሰዎች መካከል ይኑር አይኑር ዘገባው የሚገልጸው ነገር የለም።