የግርጌ ማስታወሻ
b በመሠረቱ የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎችን ለሌሎች የመስጠት ሥልጣን የነበራቸው ሐዋርያት ናቸው። በዚህ ጊዜ ግን ኢየሱስ ይህን ሥልጣን ለሐናንያ የሰጠው ይመስላል፤ በመሆኑም በዚህ ለየት ያለ ሁኔታ ሳኦል የመንፈስ ቅዱስን ስጦታዎች የተቀበለው ከሐናንያ ነው። ሳኦል ክርስትናን ከተቀበለ በኋላ ረዘም ላለ ጊዜ ከ12ቱ ሐዋርያት ጋር አልተገናኘም። ይሁንና በእነዚህ ጊዜያት ሁሉ የስብከቱን ሥራ በትጋት ሲያከናውን እንደቆየ ግልጽ ነው። በመሆኑም ኢየሱስ፣ ሳኦል የስብከት ተልእኮውን በጽናት ለመወጣት የሚያስችለውን ኃይል እንዲያገኝ ፈልጎ እንደነበር መረዳት ይቻላል።