የግርጌ ማስታወሻ
c አርዮስፋጎስ ከአክሮፖሊስ በስተ ሰሜን ምዕራብ የሚገኝ ቦታ ነው፤ የአቴንስ አስተዳዳሪዎች ሸንጎ የሚሰበሰበው እዚያ ነበር። “አርዮስፋጎስ” የሚለው ቃል ሸንጎውን አሊያም ራሱን ኮረብታውን ሊያመለክት ይችላል። ታዲያ ጳውሎስ የተወሰደው ወደዚህ ኮረብታ ወይም በአቅራቢያው ወደሚገኝ ስፍራ ነው? ወይስ ይህ አገላለጽ በሌላ ቦታ ምናልባትም በገበያ ስፍራው በተሰየመ ሸንጎ ፊት እንደቀረበ የሚጠቁም ነው? ይህን ጉዳይ በተመለከተ ምሁራን የተለያየ አመለካከት አላቸው።