የግርጌ ማስታወሻ
c አንዳንድ ምሁራን፣ እነዚህ ሰዎች የናዝራዊነት ስእለት እንደነበረባቸው ይናገራሉ። (ዘኁ. 6:1-21) እርግጥ ነው፣ ይህን ስእለት የሚያካትተው የሙሴ ሕግ አሁን ተሽሯል። ይሁንና እነዚህ ሰዎች የተሳሉት ለይሖዋ በመሆኑ ጳውሎስ ስእለቱን መፈጸማቸው ስህተት እንዳልሆነ አስቦ ሊሆን ይችላል። በመሆኑም የሰዎቹን ወጪ መክፈሉና አብሯቸው መሄዱ ምንም ስህተት የለውም። ሰዎቹ የተሳሉት ምን ዓይነት ስእለት እንደሆነ በእርግጠኝነት ማወቅ አንችልም። ይሁንና ብዙውን ጊዜ ናዝራውያን ከኃጢአት ለመንጻት የእንስሳት መሥዋዕት ያቀርቡ እንደነበር ይታወቃል፤ የሰዎቹ ስእለት ምንም ዓይነት ይሁን፣ ጳውሎስ እንዲህ ያለውን መሥዋዕት ለማቅረብ እንደማይስማማ ጥያቄ የለውም። ፍጹም የሆነው የክርስቶስ መሥዋዕት ከቀረበ ወዲህ የእንስሳት መሥዋዕቶች ኃጢአትን ማስተሰረይ አይችሉም። ጳውሎስ ያደረገው ነገር ምንም ይሁን ምን፣ ሕሊናውን የሚያስጥስ ነገር ለማድረግ እንደማይስማማ እርግጠኞች መሆን እንችላለን።