የግርጌ ማስታወሻ
a የመጀመሪያው የእንግሊዝኛ እትም ሲዘጋጅ የግሪክኛውን ጽሑፍ ለመተርጎም በዋነኝነት ያገለገለው በዌስትኮትና ሆርት የተዘጋጀው ዘ ኒው ቴስታመንት ኢን ዚ ኦሪጅናል ግሪክ የተባለው መጽሐፍ ነው። የዕብራይስጥ ቅዱሳን መጻሕፍትን ለመተርጎም በዋነኝነት ያገለገለው ደግሞ በሩዶልፍ ኪትል የተዘጋጀው ቢብሊያ ሂብራይካ ነው። ከዚህ በተጨማሪ በ2013 ታርሞ የወጣው መጽሐፍ ቅዱስ ሲዘጋጅ በሁለተኛውና በሦስተኛው መቶ ዘመን ዓ.ም. እንደተዘጋጁ የሚታመኑ ሌሎች ቀደምት የፓፒረስ ጽሑፎች ጥቅም ላይ ውለዋል። ከዚህም ሌላ በኔልሰንና አላንድ እንዲሁም በተባበሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበራት እንደተዘጋጁት ያሉትን በቅርቡ የተደረሰባቸውን ጥናታዊ ግኝቶች ያካተቱ ቅጂዎችን ለማመሳከር ጥረት ተደርጓል።