የግርጌ ማስታወሻ
f ከኢየሩሳሌም ውጭ ቆሻሻ የሚቃጠልበት ቦታ ነው። ከጥንቷ ኢየሩሳሌም በስተ ደቡብና በስተ ደቡብ ምዕራብ ይገኝ ለነበረው ለሂኖም ሸለቆ የተሰጠ ከግሪክኛ ቃል የተገኘ ስም ነው። እንስሳት ወይም ሰዎች በሕይወት እያሉ ወደዚያ ተጥለው እንዲቃጠሉ ወይም እንዲሠቃዩ ይደረግ እንደነበር የሚጠቁም ምንም ማስረጃ የለም። በመሆኑም የሰው ነፍስ ለዘላለም በእሳት የሚሠቃይበት በዓይን የማይታይ ቦታ እንደሆነ ተደርጎ መገለጹ ተገቢ አይደለም። ከዚህ ይልቅ ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ዘላለማዊ ቅጣትን ይኸውም ዘላለማዊ ጥፋትን ለማመልከት በምሳሌያዊ መንገድ ተጠቅመውበታል።