የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች

የግርጌ ማስታወሻ

a በሦስተኛው መቶ ዘመን እዘአ ተርቱልያን “ቆዳቸውን በመድኃኒት የሚያሹ፣ ጉንጫቸውን ቀይ ቀለም የሚቀቡ፣ ዐይናቸውን ኩል የሚቀቡ ሴቶች በአምላክ ላይ ኃጢአት ይሠራሉ” ብሎ ይናገር ነበር። ጸጉራቸውን ቀለም የሚቀቡትንም ይነቅፋቸው ነበር። ተርቱልያን በማቴዎስ 5:36 ላይ ያሉትን የኢየሱስ ቃላት አለ ቦታቸው በመጠቀም “የጌታን ቃል ይሽራሉ፤ እስቲ ተመልከቱት፤ ጸጉራችን ጥቁር ወይም ነጭ መሆን ሲገባው ቢጫ ቀለም ቢቀባ ትክክል ነውን?” ሐሳቡን በመጨመር “እንዲያውም ባይገርማችሁ በዕድሜ የገፉ በመሆናቸው የሚያፍሩ ሰዎች ታገኛላችሁ፤ ስለዚህ ሽበታቸውን ጥቁር ቀለም በመቀባት ይሸፍኑታል” ብሏል። ይህ የተርቱልያን የግል አስተያየት ነበር። ይሁን እንጂ ነገሮችን አጣሞ ይመለከት ነበር። ለዚህ ሁሉ ክርክሩ መሠረት ያደረገው ሰውን ለኩነኔ ያበቃችው ሴት ስለሆነች አሁን ሴቶች “ልክ እንደ ሔዋን ሆነው መሄድ፣ ስለ መጀመሪያው ኃጢአት ማዘንና መጸጸት አለባቸው” የሚለው አመለካከት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ እንደዚያ ብሎ አይናገርም። ለሰው ዘር ኃጢአተኝነት አምላክ ተጠያቂ ያደረገው አዳምን ነው።​—ሮሜ 5:12-14፤ 1 ጢሞቴዎስ 2:13, 14

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ