የግርጌ ማስታወሻ
c ጆሴፈስ የተባለው አይሁዳዊ ታሪክ ጸሐፊ የሮማ ሠራዊት በኢየሩሳሌም ላይ ስለፈጸመው የመጀመሪያ ጥቃት (በ66 እዘአ) እንዲህ ብሎ ነበር፦ “በሌሊት አውዳሚ የሆነ አውሎ ነፋስ ተነሣ። ማዕበልና ከባድ ዝናብ ወረደ፤ የማያቋርጥ መብረቅና የሚያስፈራ ነጎድጓድ ነበር። ምድሪቱ ጆሮ የሚያደነቁር ድምፅ ባለበት ነውጥ ተመታች። ይህ አጠቃላይ የሆነ የነገሮች መዋቅር መፈራረስ የሰው ዘር እልቂት መድረሱን የሚያመለክት ጥላ እንደነበረ ግልጽ ነው። እነዚህ ምልክቶች አቻ የሌለው መዓት መምጣቱን እንደሚያመለክቱ ሊጠራጠር የሚችል ሰው አልነበረም።”