የግርጌ ማስታወሻ
b ይህ ማብራሪያ ያተኮረው ቋንቋው ነጥቡን ግልጽ ለማድረግ የሚያስችል ሆኖ ሳለ በዚህ መንገድ ለመተርጎም ባልፈለጉ ተርጓሚዎች ላይ ነው። አንዳንድ ቋንቋዎች ያሏቸው ቃላት ውስን በመሆናቸው ተርጓሚዎቹ ሐሳቡን በግልጽ ለማስቀመጥ ሊቸገሩ ይችላሉ። እንዲህ ዓይነት ሁኔታ ሲኖር ሐቀኛ ሃይማኖታዊ አስተማሪዎች ተርጓሚው የተለያዩ መግለጫዎችን ወይም ደግሞ ቅዱስ ጽሑፋዊ ቃና የሌለው አንድ ቃል ተጠቅሞ ከሆነ መጽሐፍ ቅዱስ መጀመሪያ በተጻፈበት ቋንቋ እዚህ ላይ የገባው ቃል ነፈሽ የሚለው ቃል እንደሆነና ቃሉ ሰዎችንም ሆነ እንስሳትን ለማመልከት እንደሚያገለግል እንዲሁም እስትንፋስ ያለውን፣ የሚመገብንና ሊሞት የሚችልን ፍጡር እንደሚያመለክት ያብራራሉ።