የግርጌ ማስታወሻ
a ምንም እንኳ ጳውሎስ “እንደ ደነገግሁት” ብሎ ቢናገርም፣ በራሱ አነሳሽነት የግድ እንዲያዋጡ ደንግጓል ማለት አይደለም። ከዚህ ይልቅ በርካታ ጉባኤዎች የሚያደርጉትን መዋጮ በበላይነት ይቆጣጠር ነበር ማለት ነው። ከዚህም በተጨማሪ ጳውሎስ እያንዳንዱ ሰው “በቤቱ” የሚሰጠው “እንደ ቀናው መጠን” እንዲሆን ተናግሯል። በሌላ አነጋገር ማንኛውም መዋጮ የሚደረገው በግል፣ በራስ አነሳሽነት ነበር። ማንም ሰው መዋጮ እንዲያደርግ አይገደድም ነበር።