የግርጌ ማስታወሻ
b ዮሴፍ ለመጨረሻ ጊዜ በቀጥታ የተጠቀሰው የ12 ዓመት ልጅ የነበረው ኢየሱስ በቤተ መቅደሱ ውስጥ በተገኘበት ወቅት ነው። ኢየሱስ አገልግሎቱን በጀመረበት ወቅት በቃና ተደርጎ በነበረው የሠርግ ግብዣ ላይ ዮሴፍ እንደተገኘ የሚገልጽ ማስረጃ የለም። (ዮሐንስ 2:1-3) በ33 እዘአ ኢየሱስ ተሰቅሎ ሳለ ማርያምን አደራ የሰጠው ለተወደደው ለሐዋርያው ዮሐንስ ነበር። ዮሴፍ በሕይወት የነበረ ቢሆን ኖሮ ኢየሱስ እንዲህ አያደርግም ነበር።—ዮሐንስ 19:26, 27