የግርጌ ማስታወሻ
a ላ ሳግራታ ኤስከሬቱራ—ቴክስቶ ኤ ኮሜንታርዮ ፖር ፕሮፌሶርስ ደ ላ ካምፓኒያ ደ ሄሱስ የተባለው መጽሐፍ “ሰብዓ ሰገል በፋርሳውያን፣ በሜዶናውያንና በከለዳውያን ዘንድ ምትሃታዊ ድርጊቶችን፣ ኮከብ ቆጠራንና መድኃኒት ቅመማን የሚያከናውኑ ካህናት ነበሩ” ይላል። ይሁን እንጂ ሕፃኑን ኢየሱስን ለማየት የሄዱት ሰብዓ ሰገል በመካከለኛው ዘመን “ቅዱሳን” ተብለውና ሜልክዮር፣ ጋስፓርና ባልታዛር የሚሉ ስሞች ወጥቶላቸው ነበር። አስከሬናቸውም በኮሎኝ፣ ጀርመን በሚገኝ አንድ ካቴድራል ውስጥ እንደተቀመጠ ይነገራል።