የግርጌ ማስታወሻ
a ሆዳምነት ከአስተሳሰብ ጋር የተያያዘ ነገር ነው፤ ሆዳም የሚባለው አልጠግብ ባይ ወይም ስግብግብ የሆነ ሰው ነው። በመሆኑም አንድ ግለሰብ ሆዳም መሆኑ የሚታወቀው በክብደቱ ሳይሆን ለምግብ ባለው አመለካከት ነው። መካከለኛ ሰውነት ያለው እንዲያውም ቀጭን የሆነ ሰውም እንኳ ሆዳም ሊሆን ይችላል። በሌላ በኩል ደግሞ አንዳንድ ጊዜ ከመጠን በላይ መወፈር በሕመም ምክንያት ሊመጣ አሊያም ከቤተሰብ ሊወረስ ይችላል። አንድ ሰው ወፍራምም ይሁን ቀጭን ሆዳም የሚያስብለው ከምግብ ጋር በተያያዘ ስግብግብነት የተጠናወተው መሆኑ ነው።—በኅዳር 1, 2004 መጠበቂያ ግንብ ላይ የወጣውን “የአንባቢያን ጥያቄ” ተመልከት።