የግርጌ ማስታወሻ
b አንዳንድ ምሑራን እንደሚሉት ከሆነ በዘፀአት 32:10 ላይ የሚገኘው “ተወኝ” የሚለው የዕብራይስጥ አገላለጽ ሙሴ ይሖዋንና እስራኤልን እንዲያስታርቅ ወይም ‘በመካከላቸው እንዲገባ’ የቀረበ ግብዣ እንደሆነ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። (መዝ. 106:23፤ ሕዝ. 22:30 የታረመው የ1980 ትርጉም) ይህ አስተያየት ትክክል ሆነም አልሆነ፣ ሙሴ አመለካከቱን ለይሖዋ ለመግለጽ ነፃነት እንደተሰማው መመልከት ይቻላል።