የግርጌ ማስታወሻ
c የባቢሎን ነገሥታት “የግዛት ዘመን” የሚቆጠረው ከኒሳን ወር እስከ ኒሳን ወር ነበር። አንድ ንጉሥ የመጨረሻ “የግዛት ዘመኑን” ሳያጠናቅቅ በሚሞትበት ጊዜ አልጋ ወራሹ ሥልጣን ላይ ወጥቶ በቀሪዎቹ ወራት በመግዛት የሟቹን የግዛት ዘመን ያጠናቅቅለታል። ይህ ወቅት የአዲሱ ንጉሥ “የሽግግር ዘመን” ተብሎ ይጠራል። “የሽግግር ዘመን” የሚለው አገላለጽ አዲሱ ንጉሥ በይፋ ሥልጣን እስከሚይዝበት ጊዜ ድረስ (ይኸውም እስከ ቀጣዩ ዓመት ኒሳን ወር ድረስ) ያሉትን ወራት ያመለክታል። በመሆኑም የአዲሱ ንጉሥ “የግዛት ዘመን” እስከ ቀጣዩ ኒሳን ድረስ አይጀምርም።