የግርጌ ማስታወሻ
a በዚህ ዓምድ ሥር ከዚህ ቀደም በወጣው ርዕስ ላይ ወላጆቿ የሞቱባትን አስቴርን መርዶክዮስ የሚባል በዕድሜ የሚበልጣት የአጎቷ ልጅ እንዳሳደጋትና ከጊዜ በኋላም የፋርሱ ንጉሥ የጠረክሲስ ሚስት ለመሆን እንደተመረጠች አይተን ነበር። የንጉሡ አማካሪ የነበረው ሐማ የመርዶክዮስ ሕዝብ የሆኑትን አይሁዳውያንን ለመደምሰስ አንድ ክፉ ሴራ ጠንስሶ ነበር። በመሆኑም አስቴር ወደ ንጉሡ ቀርባ ሕዝቧ እንዳይጠፋ ልመና እንድታቀርብ መርዶክዮስ ጠይቋታል።—በጥቅምት 1, 2011 መጠበቂያ ግንብ ላይ የወጣውን “በእምነታቸው ምሰሏቸው—ለአምላክ ሕዝብ ጥብቅና ቆማለች” የሚለውን ርዕስ ተመልከት።