የግርጌ ማስታወሻ
b የጥንት ጸሐፊዎች በዚህ ጥቅስ ላይ ያለውን “ነፍስህ” የሚለውን ቃል “ነፍሴ” በሚለው በመቀየር ኤርምያስን እንዲያመለክት አድርገው አስቀምጠውታል። ይህን ያደረጉት መጽሐፍ ቅዱስ በምድር ያሉ ፍጥረታትን ለማመልከት የሚጠቀምበትን ነፍስ የሚለውን ቃል ለአምላክ መጠቀም እሱን አለማክበር እንደሆነ ተሰምቷቸው መሆን አለበት። ይሁንና ስለ አምላክ መረዳት እንድንችል ሲባል ብዙውን ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አምላክ የተገለጸው ሰዎች በቀላሉ በሚገባቸው መንገድ ነው። “ነፍስ” የሚለው ቃል “ሕይወታችንን” ሊያመለክት ስለሚችል “ነፍስህ” የሚለው ቃል በዚህ አገባቡ “አንተ” ማለት ነው።