የግርጌ ማስታወሻ
a የአምላክ ስም በተለምዶ ብሉይ ኪዳን እየተባለ በሚጠራው የዕብራይስጥ ቅዱሳን መጻሕፍት ክፍል ውስጥ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል፤ የሚያሳዝነው ግን ይህ ስም ከብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ውስጥ እንዲወጣ ተደርጓል። ተርጓሚዎቹ የአምላክን ስም “ጌታ” ወይም “አምላክ” እንደሚሉት ባሉ የማዕረግ መጠሪያዎች ተክተውታል። ስለዚህ ጉዳይ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በይሖዋ ምሥክሮች የተዘጋጀውን ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው? የተባለውን መጽሐፍ ከገጽ 195-197 ተመልከት።