የግርጌ ማስታወሻ
a አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሑራን፣ ይሁዳ ይህን ሐሳብ የወሰደው መጽሐፈ ሄኖክ ከሚባል አንድ የአዋልድ መጽሐፍ እንደሆነ ይናገራሉ፤ ይህ የአዋልድ መጽሐፍ ምንጩ ያልታወቀና እውነት የማይመስሉ ታሪኮችን የያዘ ከመሆኑም ሌላ ሄኖክ እንደጻፈው ተደርጎ መነገሩ ሐሰት ነው። መጽሐፉ የሄኖክን ትንቢት በትክክል የሚጠቅስ ቢሆንም ይህ ሐሳብ የተወሰደው አሁን ከጠፋ ጥንታዊ ጽሑፍ ላይ ወይም በቃል ሲተላለፍ ከቆየ ታሪክ ሊሆን ይችላል። ይሁዳም ይህን ትንቢት ያገኘው ከተመሳሳይ ምንጭ ሊሆን ይችላል፤ አሊያም ደግሞ የሄኖክን ሕይወት ከሰማይ ሆኖ የተመለከተው ኢየሱስ ነግሮት ሊሆን ይችላል።