የግርጌ ማስታወሻ
d የሥዕሉ መግለጫ፦ በስብሰባ አዳራሾቻችን ውስጥ የምናደርጋቸው ስብሰባዎች ለሌሎች ያለንን ፍቅር የምናሳይበት ሰፊ አጋጣሚ ይሰጡናል። በሥዕሉ ላይ (1) አንድ ሽማግሌ፣ አስፋፊ የሆነን አንድ ትንሽ ልጅና እናቱን በደግነት ሲያነጋግራቸው፣ (2) አንድ አባትና ሴት ልጁ አንዲት አረጋዊ እህትን ወደ መኪና ይዘዋቸው ሲሄዱ፣ (3) ሁለት ሽማግሌዎች እርዳታ ማግኘት የምትፈልግን አንዲት እህት በጥሞና ሲያዳምጧት ይታያል።