የግርጌ ማስታወሻ
a አንድ ቤተሰብ ደስተኛ እንዲሆን እያንዳንዱ የቤተሰቡ አባል የሚጠበቅበትን ነገር ማወቅ እንዲሁም ከሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት ጋር መተባበር ይኖርበታል። አባትየው ቤተሰቡን በፍቅር ይመራል፤ እናትየዋ አባትየውን ትደግፈዋለች፤ ልጆቹ ደግሞ ወላጆቻቸውን ይታዘዛሉ። ከይሖዋ ቤተሰብ ጋር በተያያዘም ሁኔታው ተመሳሳይ ነው። አምላካችን ለእኛ ዓላማ አለው፤ ከዚህ ዓላማ ጋር ተባብረን የምንሠራ ከሆነ የይሖዋን አምላኪዎች ባቀፈው ቤተሰብ ውስጥ ለዘላለም መኖር እንችላለን።