የግርጌ ማስታወሻ
a ይሖዋን ለረጅም ጊዜ ያገለገለ አንድ ክርስቲያን “ይህ ሥርዓት ይህን ያህል ይቆያል ብዬ አላሰብኩም ነበር” ሲል ሰምተህ ታውቃለህ? ያለንበት ጊዜ በጣም አስቸጋሪ ከመሆኑ አንጻር ሁላችንም ይሖዋ ይህን ክፉ ሥርዓት የሚያጠፋበትን ጊዜ በጉጉት እንጠብቃለን። ያም ቢሆን ታጋሾች መሆን አለብን። በትዕግሥት እንድንጠብቅ የሚረዱንን የመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ ሥርዓቶች በዚህ ርዕስ ውስጥ እንመለከታለን። በተጨማሪም በየትኞቹ ሁለት ሁኔታዎች ውስጥ ይሖዋን በትዕግሥት መጠበቅ እንዳለብን እንመረምራለን። በመጨረሻም በትዕግሥት የሚጠብቁ ሰዎች የሚያገኟቸውን በረከቶች እናያለን።