የግርጌ ማስታወሻ
b የሥዕሉ መግለጫ፦ አንዲት እህት ከልጅነቷ አንስቶ አዘውትራ ወደ ይሖዋ ትጸልያለች። ትንሽ ልጅ ሳለች ወላጆቿ እንዴት መጸለይ እንዳለባት አስተምረዋታል። በወጣትነቷ አቅኚ ሆና ማገልገል ጀመረች፤ ይሖዋ አገልግሎቷን እንዲባርክላት አዘውትራ ትጠይቀው ነበር። ከዓመታት በኋላ ባለቤቷ በጠና ሲታመም ይህን ፈተና ለመቋቋም የሚያስችላትን ኃይል እንዲሰጣት ወደ ይሖዋ ምልጃ ስታቀርብ ይታያል። በአሁኑ ወቅት መበለት ናት፤ የሰማዩ አባቷ ከልጅነቷ ጀምሮ ሲያደርግላት እንደነበረው አሁንም ጸሎቷን እንደሚመልስላት በመተማመን በጽናት ትጸልያለች።