የግርጌ ማስታወሻ
c ከዚህ ቀደም፣ እዚህ ጥቅስ ላይ ያለው “ፍርድ” የሚለው ቃል እነዚህ ሰዎች እንደሚፈረድባቸው ወይም አሉታዊ ፍርድ እንደሚሰጣቸው እንደሚያመለክት ገልጸን ነበር። እርግጥ “ፍርድ” የሚለው ቃል ይህን ትርጉም ሊያስተላልፍ ይችላል። ሆኖም በዚህ ጥቅስ ላይ ኢየሱስ “ፍርድ” የሚለውን ቃል ጠቅለል ባለ መልኩ ማለትም የግምገማ ወይም የፈተና ሂደትን ለማመልከት የተጠቀመበት ይመስላል፤ አንድ የግሪክኛ መዝገበ ቃላት፣ ይህ ቃል ‘የአንድን ሰው ምግባር መፈተንን’ ሊያመለክት እንደሚችል ይገልጻል።