የግርጌ ማስታወሻ
a ለ2023 እምነት የሚያጠናክር የዓመት ጥቅስ ተመርጦልናል፦ “የቃልህ ፍሬ ነገር እውነት ነው።” (መዝ. 119:160) እናንተም በዚህ ሐሳብ እንደምትስማሙ ምንም ጥያቄ የለውም። ሆኖም ብዙ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስ እውነትና አስተማማኝ መመሪያ የያዘ መሆኑን አያምኑም። ቅን ልብ ያላቸው ሰዎች በመጽሐፍ ቅዱስና በውስጡ ባለው ምክር እንዲተማመኑ ለመርዳት ልንጠቀምባቸው የምንችላቸውን ሦስት ማስረጃዎች በዚህ ርዕስ ላይ እንመለከታለን።