የግርጌ ማስታወሻ
a ኃይለኛ ማዕበልን ጸጥ አሰኝቷል፤ የታመሙትን ፈውሷል፤ የሞቱትንም አስነስቷል። በእርግጥም ኢየሱስ ስለፈጸማቸው ተአምራት ማንበብ እጅግ ያስደስታል። እነዚህ ዘገባዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሰፈሩልን እንዲያዝናኑን ሳይሆን እንዲያስተምሩን ነው። እነዚህን ዘገባዎች መለስ ብለን ስንመረምር ይሖዋንና ኢየሱስን በተመለከተ እምነት የሚያጠናክሩ ትምህርቶች እናገኛለን። እንዲሁም ልናዳብራቸው ስለሚገቡ ግሩም ክርስቲያናዊ ባሕርያት እንማራለን።