የግርጌ ማስታወሻ
a ለምሳሌ ያህል፣ የዩናይትድ ስቴትስ የጤናና የሰብዓዊ አገልግሎቶች ክፍል ባወጣው ደረጃ መሠረት ከልክ ያለፈ የመጠጥ አወሳሰድ የሚባለው “ለሴቶች በቀን 4 ወይም ከዚያ በላይ መጠጣት ወይም በሳምንት 8 ወይም ከዚያ በላይ መጠጣት፣ ለወንዶች ደግሞ በቀን 5 ወይም ከዚያ በላይ መጠጣት ወይም በሳምንት 15 ወይም ከዚያ በላይ መጠጣት ነው።” መደበኛ ተብሎ የሚወሰነው የመጠጥ መጠን ከአገር አገር ሊለያይ ይችላል፤ በመሆኑም በአካባቢህ ያለው የጤና ጥበቃ ባለሥልጣን፣ ልከኛ ነው የሚለው የመጠጥ አወሳሰድ ምን ያህል እንደሆነ አጣራ።