የግርጌ ማስታወሻ
b አንዳንዶች “የአምላክ ልጅ” የሚለው አገላለጽ አምላክ ከሴት ጋር ግንኙነት እንደፈጸመ የሚያመለክት እንደሆነ ስለሚሰማቸው ይህን አገላለጽ መጠቀም ተገቢ እንዳልሆነ ይናገራሉ። ሆኖም መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ አይልም። እንዲያውም ኢየሱስ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ “የአምላክ ልጅ” እንዲሁም “የፍጥረት ሁሉ በኩር” ተብሎ ተጠርቷል፤ ይህ መጠሪያ የተሰጠው በቀጥታ በአምላክ የተፈጠረው የመጀመሪያውና ብቸኛው አካል እሱ ስለሆነ ነው። (ቆላስይስ 1:13-15) በተጨማሪም መጽሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያውን ሰው አዳምን “የአምላክ ልጅ” በማለት ይጠራዋል። (ሉቃስ 3:38) አዳም እንዲህ ተብሎ የተጠራው በአምላክ ስለተፈጠረ ነው።