የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ረቡዕ፣ ሐምሌ 16

ይሖዋ የጥበበኞች ሐሳብ ከንቱ እንደሆነ ያውቃል።—1 ቆሮ. 3:20

ከሰብዓዊ አስተሳሰብ መራቅ ይኖርብናል። ነገሮችን በሰብዓዊ ዓይን መመልከት ከጀመርን ይሖዋንና መሥፈርቶቹን ችላ ልንል እንችላለን። (1 ቆሮ. 3:19) “የዚህ ዓለም ጥበብ” በአብዛኛው ለኃጢአተኛው ሥጋችን የሚማርክ ነው። አንዳንድ የጴርጋሞንና የትያጥሮን ክርስቲያኖች በከተሞቹ በተስፋፋው ጣዖት አምልኮና የብልግና አኗኗር ተስበው ነበር። የፆታ ብልግናን በቸልታ በማለፋቸው ኢየሱስ ለሁለቱም ጉባኤዎች ጠንከር ያለ ምክር ሰጥቷቸዋል። (ራእይ 2:14, 20) በዛሬው ጊዜም የዓለምን የተሳሳተ አመለካከት እንድንቀበል ጫና ይደረግብናል። የቤተሰባችን አባላትና የምናውቃቸው ሰዎች ሊያባብሉንና አቋማችንን እንድናላላ ሊያሳምኑን ይሞክሩ ይሆናል። ለምሳሌ፣ ለምኞታችን እጅ መስጠት ምንም ችግር እንደሌለው ወይም የመጽሐፍ ቅዱስ የሥነ ምግባር መሥፈርቶች ጊዜ ያለፈባቸው እንደሆኑ ይናገሩ ይሆናል። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የይሖዋ መመሪያዎች በበቂ መጠን ግልጽ እንዳልሆኑ እናስብ ይሆናል። ይባስ ብሎም ‘ከተጻፈው ለማለፍ’ ልንፈተን እንችላለን።—1 ቆሮ. 4:6፤ w23.07 16 አን. 10-11

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ሐሙስ፣ ሐምሌ 17

እውነተኛ ወዳጅ ምንጊዜም አፍቃሪ ነው፤ ደግሞም ለመከራ ቀን የተወለደ ወንድም ነው።—ምሳሌ 17:17

የኢየሱስ እናት ማርያም ጥንካሬ አስፈልጓት ነበር። ማርያም አላገባችም፤ ሆኖም እንደምትፀንስ ተነገራት። የራሷን ልጆች አሳድጋ አታውቅም፤ ሆኖም መሲሑን ማሳደግ ሊኖርባት ነው። ደግሞም ከወንድ ጋር ግንኙነት ሳትፈጽም ስላረገዘች ሁኔታውን ለእጮኛዋ ለዮሴፍ እንዴት ልታብራራለት ትችላለች? (ሉቃስ 1:26-33) ማርያም ጥንካሬ ያገኘችው እንዴት ነው? የሌሎችን እርዳታ ለማግኘት ጥረት አድርጋለች። ለምሳሌ የተሰጣትን ኃላፊነት አስመልክቶ ተጨማሪ መረጃ እንዲሰጣት ገብርኤልን ጠይቃዋለች። (ሉቃስ 1:34) ከዚያ ብዙም ሳይቆይ ደግሞ ዘመዷን ኤልሳቤጥን ለመጠየቅ ረጅም መንገድ ተጉዛ “በተራራማው አገር” ወደምትገኝ አንዲት የይሁዳ ከተማ ሄዳለች። ኤልሳቤጥ ማርያምን አመሰገነቻት፤ እንዲሁም በይሖዋ መንፈስ ተመርታ በማርያም ማኅፀን ውስጥ ያለውን ልጅ በተመለከተ የሚያበረታታ ትንቢት ተናገረች። (ሉቃስ 1:39-45) ማርያም፣ ይሖዋ ‘በክንዱ ታላላቅ ሥራዎች እንዳከናወነ’ ገልጻለች። (ሉቃስ 1:46-51) ይሖዋ በገብርኤልና በኤልሳቤጥ አማካኝነት ማርያምን አጠንክሯታል። w23.10 14-15 አን. 10-12

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ዓርብ፣ ሐምሌ 18

ነገሥታት እንዲሁም ለአምላኩና ለአባቱ ካህናት [አደረገን]።—ራእይ 1:6

የተወሰነ ቁጥር ያላቸው የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት በመንፈስ ቅዱስ ተቀብተዋል፤ እነዚህ ሰዎች ከይሖዋ ጋር ልዩ ዝምድና አላቸው። እነዚህ 144,000 ሰዎች በሰማይ ከኢየሱስ ጋር ካህናት ሆነው ያገለግላሉ። (ራእይ 14:1) ቅድስት የተባለው የማደሪያ ድንኳኑ ክፍል ቅቡዓን ክርስቲያኖች ገና ምድር ላይ ሳሉ ያሉበትን ሁኔታ ማለትም በመንፈስ የተወለዱ የአምላክ ልጆች መሆናቸውን ያመለክታል። (ሮም 8:15-17) ቅድስተ ቅዱሳን የተባለው የማደሪያ ድንኳኑ ክፍል ደግሞ ይሖዋ የሚኖርበትን ሰማይን ያመለክታል። ቅድስቱንና ቅድስተ ቅዱሳኑን የሚለየው “መጋረጃ” ኢየሱስ የመንፈሳዊው ቤተ መቅደስ ታላቅ ሊቀ ካህናት ሆኖ ወደ ሰማይ እንዳይገባ ያገደውን ሥጋዊ አካሉን ያመለክታል። ኢየሱስ ሰብዓዊ አካሉን ለሰው ልጆች መሥዋዕት አድርጎ በማቅረብ ሁሉም ቅቡዓን ክርስቲያኖች ሰማያዊ ሕይወት ማግኘት የሚችሉበትን መንገድ ከፍቷል። እነሱም ቢሆኑ ሰማያዊ ሽልማታቸውን ለመቀበል ሥጋዊ አካላቸውን መተው ይጠበቅባቸዋል።—ዕብ. 10:19, 20፤ 1 ቆሮ. 15:50፤ w23.10 28 አን. 13

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ