የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ዓርብ፣ ነሐሴ 29

ስምህን አሳውቄአቸዋለሁ።—ዮሐ. 17:26

ኢየሱስ ለሰዎች የአምላክ ስም ይሖዋ መሆኑን ከማሳወቅ ያለፈ ነገር አድርጓል። ኢየሱስ ያስተማራቸው አይሁዳውያን ቀድሞውንም የአምላክን ስም ያውቃሉ። ሆኖም ኢየሱስ ግንባር ቀደም ሆኖ ስለ እሱ ‘ገልጿል።’ (ዮሐ. 1:17, 18) ለምሳሌ የዕብራይስጥ ቅዱሳን መጻሕፍት ይሖዋ መሐሪና ሩኅሩኅ እንደሆነ ይናገራሉ። (ዘፀ. 34:5-7) ኢየሱስ ስለ አባካኙ ልጅና ስለ አባቱ የሚገልጸውን ምሳሌ በተናገረበት ወቅት ይህንን እውነት ይበልጥ ግልጽ አድርጎታል። አባትየው ንስሐ የገባውን ልጁን ‘ገና ሩቅ ሳለ እንዳየው፣’ ሮጦ ሄዶ እንደተቀበለው፣ እንዳቀፈው እንዲሁም በሙሉ ልቡ ይቅር እንዳለው ስናነብ የይሖዋ ምሕረትና ርኅራኄ ግልጽ ሆኖ ይታየናል። (ሉቃስ 15:11-32) በእርግጥም ኢየሱስ የአባቱን እውነተኛ ማንነት ገልጦልናል። w24.02 10 አን. 8-9

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ቅዳሜ፣ ነሐሴ 30

ከአምላክ በምናገኘው መጽናኛ [ሰዎችን እናጽናና]።—2 ቆሮ. 1:4

ይሖዋ የተጨነቁ ሰዎችን ያጽናናል። ለሌሎች በመራራትና እነሱን በማጽናናት ይሖዋን መምሰል የምንችለው እንዴት ነው? ይህን ማድረግ የምንችልበት አንዱ መንገድ ማጽናኛ ለመስጠት የሚያነሳሱ ባሕርያትን በልባችን ውስጥ በማዳበር ነው። ከእነዚህ ባሕርያት መካከል አንዳንዶቹ የትኞቹ ናቸው? ‘ሁልጊዜ እርስ በርስ ለመጽናናት’ የሚያነሳሳ ፍቅር እንዲኖረን ምን ይረዳናል? (1 ተሰ. 4:18) የሌላውን ስሜት መረዳት እንዲሁም የወንድማማች መዋደድንና ደግነትን የመሳሰሉ ባሕርያትን ማዳበር ይኖርብናል። (ቆላ. 3:12፤ 1 ጴጥ. 3:8) እነዚህ ባሕርያት የሚረዱን እንዴት ነው? ርኅራኄ እና ተመሳሳይ ባሕርያት የማንነታችን ክፍል ከሆኑ የተጨነቁ ሰዎችን እንድናጽናና ውስጣችን ይገፋፋናል። ኢየሱስ እንዳለው “አንደበት የሚናገረው በልብ ውስጥ የሞላውን ነውና። ጥሩ ሰው በልቡ ካከማቸው መልካም ነገር ጥሩ ነገር ያወጣል።” (ማቴ. 12:34, 35) በእርግጥም እርዳታ የሚያስፈልጋቸውን ወንድሞቻችንን እና እህቶቻችንን ማጽናናት ለእነሱ ያለንን ፍቅር የምንገልጽበት ወሳኝ መንገድ ነው። w23.11 10 አን. 10-11

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

እሁድ፣ ነሐሴ 31

ጥልቅ ማስተዋል ያላቸው . . . ይረዱታል።—ዳን. 12:10

የመጽሐፍ ቅዱስን ትንቢቶች መረዳት ከፈለግን እርዳታ መጠየቅ ይኖርብናል። አንድ ምሳሌ እንመልከት። ጨርሶ የማታውቀውን ቦታ ለመጎብኘት አስበሃል እንበል። ሆኖም አብሮህ የሚጓዘው ጓደኛህ አካባቢውን በደንብ ያውቀዋል። የት እንዳላችሁ እንዲሁም እያንዳንዱ መንገድ ወዴት እንደሚያመራ ጠንቅቆ ያውቃል። ጓደኛህ አብሮህ ለመምጣት በመስማማቱ በጣም እንደምትደሰት ጥያቄ የለውም። በተመሳሳይም ይሖዋ በጊዜ ሰሌዳ ላይ የቱ ጋ እንዳለን እንዲሁም ወደፊት ምን እንደሚጠብቀን ያውቃል። በመሆኑም የመጽሐፍ ቅዱስን ትንቢቶች መረዳት ከፈለግን ይሖዋ እንዲረዳን በትሕትና ልንጠይቀው ይገባል። (ዳን. 2:28፤ 2 ጴጥ. 1:19, 20) እንደ ማንኛውም ጥሩ ወላጅ፣ ይሖዋ ልጆቹ ወደፊት ደስተኛ ሕይወት እንዲመሩ ይፈልጋል። (ኤር. 29:11) ሆኖም ከሰብዓዊ ወላጆች በተለየ መልኩ ይሖዋ ስለ ወደፊቱ ጊዜ በትክክል ትንቢት መናገር ይችላል። ወሳኝ የሆኑ ክንውኖች ከመከሰታቸው በፊት እንድናውቅ ሲል ትንቢቶች በቃሉ ውስጥ እንዲሰፍሩ አድርጓል።—ኢሳ. 46:10፤ w23.08 8 አን. 3-4

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ