መዝሙር 106
የይሖዋ ወዳጅ መሆን
በወረቀት የሚታተመው
(መዝሙር 15)
1. ያንተ ወዳጅ ማን ነው?
በድንኳንህ ’ሚያድረው?
በደንብ የሚያውቅህ፣ የምታምነው፣
ያንተ ወዳጅ ማን ነው?
ቃልህን የሚወድ፣
ባንተ የሚታመን፣
ጥሩና ታማኝ የሆነ ሰው፣
ላንተ ’ሚሰጥ ራሱን።
2. ያንተ ወዳጅ ማን ነው?
ዙፋንህ ’ሚቀርበው?
ደስ የምትሰኝበትና
በስም የምታውቀው?
ስምህን ’ሚያወድስ፣
ቃልህን ’ሚጠብቅ፣
ሁሌም ሐቀኛ የሆነ ሰው፣
ከመዋሸት ’ሚርቅ።
3. የሚያስጨንቀንን
በጸሎት ስንነግርህ፣
’ሚያስፈልገንን ታሟላለህ፤
ስቦናል ይህ ፍቅርህ።
ሁሌም ያንተ ወዳጅ
መሆን ያጓጓናል፤
ከዚህ የሚበልጥ ወዳጅነት
ከወዴት ይገኛል?
(በተጨማሪም መዝ. 139:1ን እና 1 ጴጥ. 5:6, 7ን ተመልከት።)