የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “በመማፀኛው ከተማ” ውስጥ ቆይተህ ሕይወትህን አድን!
    መጠበቂያ ግንብ—1995 | ኅዳር 15
    • 20. በታላቁ የመማፀኛ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ከደም ተበቃዩ ለመዳን ምን ማድረግ ይኖርባቸዋል?

      20 በስሕተት ነፍስ የገደለ ግለሰብ ከደም ተበቃዩ ለመዳን በመማፀኛ ከተማው ውስጥ መቆየት ነበረበት። ከግጦሽ ሥፍራዎቹ ርቆ መሄድ አልነበረበትም። በታላቁ የመማፀኛ ከተማ ውስጥ ስለሚኖሩ ሰዎችስ ምን ለማለት ይቻላል? ከታላቁ ደም ተበቃይ እንዲድኑ ከተማውን ለቅቀው መውጣት የለባቸውም። በምሳሌያዊ አነጋገር ወደ ግጦሽ ስፍራዎቹ ወሰን እንዲሄዱ ከሚያደርጓቸው ማታለያዎች መጠንቀቅ ያስፈልጋቸዋል። ልባቸው ለሰይጣን ዓለም ፍቅር እንዳያድርበት ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል። ይህ ጸሎትንና ጥረትን የሚጠይቅ ሊሆን ቢችልም ሕይወታቸው የተመካው በዚህ ላይ ነው።—1 ዮሐንስ 2:15–17፤ 5:19

  • የመዋለድና የጦርነት ሴት አማልክት
    መጠበቂያ ግንብ—1995 | ኅዳር 15
    • የመዋለድና የጦርነት ሴት አማልክት

      ሶርያ ውስጥ ኢብል በተባለው ቦታ አርኪኦሎጂያዊ ቁፋሮ በሚካሄድበት ወቅት ኢሽታር ተብላ የምትጠራው የባቢሎናውያን የመዋለድና የጦርነት አምላክ ምስል ተገኘ። ፓኦሎ ማቲ የተባሉ አርኪኦሎጂስት ምስሉን እንደዚህ በማለት ገልጸውታል፦ “ጥምጣም ያደረጉ ካህናት በአንድ የመለኮት ምስል ፊት ቆመው የሚያሳይ ክብ ቅርፅ ያለው የአምልኮ ምስል ነው። . . . የምስሉ ራስ ረጅምና ቀጭን ከሆነ ድጋፍ ጋር ተጣብቋል።”

      ምስሉ በ18ኛው መቶ ዘመን ከዘአበ መጀመሪያ ላይ የነበረ ስለሆነ ግኝቱ ትልቅ ግምት የሚሰጠው ነው። ማቲ እንደተናገሩት ይህ ምስል የኢሽታር አምልኮ የ2,000 ዓመት እድሜ እንዳለው “የማያዳግም ማረጋገጫ” ይሰጣል።

      የኢሽታር አምልኮ የተጀመረው በባቢሎን ሲሆን በተከታዮቹ መቶ ዓመታት በመላው የሮማ ግዛት ተሰራጭቷል። እስራኤላውያን ማንኛውንም የሐሰት ሃይማኖት ርዝራዥ ከተስፋይቱ ምድር እንዲያስወግዱ ይሖዋ አዝዞ ነበር። ቢሆንም ይህንን ትእዛዝ ስላልተከተሉ የአስታሮት አምልኮ (ከኢሽታር ጋር የምትመሳሰል የከነዓናውያን ጣዖት) ወጥመድ ሆነባቸው።—ዘዳግም 7:2, 5፤ መሳፍንት 10:6

      ምንም እንኳ ኢሽታርና እኩያዋ አስታሮት በአሁኑ ጊዜ ባይኖሩም መለያቸው የሆነው ብልግና እና ዓመፅ አሁንም በሰፊው አለ። ዘመናዊው ኅብረተሰብ እነዚህን የመዋለድና የጦርነት ሴት አማልክት ያመልኩ የነበሩ ሰዎች ከነበሩበት የጥንቱ ሥልጣኔ ምኑን ተለየው ብለን እንገረም ይሆናል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ