የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ሐሰተኛ ነቢያት
    ከቅዱሳን ጽሑፎች እየጠቀሱ ማመራመር
    • አንድ ሰው እንዲህ ቢልስ:-

      ‘የይሖዋ ምሥክሮች ሐሰተኛ ነቢያት ናቸው ብለው ቄሶች ነግረውናል’

      እንዲህ በማለት ልትመልስ ትችላለህ:- ‘አንድ ጥያቄ ብጠይቅዎትስ? በምን እንደምናምን ወይም ምን እንደምንሠራና በዚህም ምክንያት ሐሰተኛ ነቢያት መሆናችንን የሚያሳይ ቃል ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሳይተዋችኋል? . . . መጽሐፍ ቅዱስ ሐሰተኛ ነቢያትን እንዴት አድርጎ እንደሚገልጻቸው ባሳይዎትስ? (በገጽ 133–136 ከተገለጹት ነጥቦች በአንዱ ወይም ከዚያ በላይ ተጠቀም።)’

      ወይም እንዲህ ማለት ትችላለህ:- ‘እንደዚህ የመሰለው ከባድ ክስ ግልጽ በሆነ መረጃ መደገፍ አለበት ቢባል እንደሚስማሙ እርግጠኛ ነኝ። ቄሶቹ እንደ ምሳሌ አድርገው የጠቀሱላችሁ ግልጽ የሆነ ነገር አለ? (የቤቱ ባለቤት ይፈጸማሉ ተብለው ሳይፈጸሙ ቀርተዋል የሚባሉ “ትንበያዎችን” የሚጠቅሱ ከሆነ በገጽ 135ና ከገጽ 136 መጀመሪያ እስከ ገጽ 137 መጨረሻ በቀረበው ሐሳብ ተጠቀም።)’

      ሌላ አማራጭ:- ‘አንድ ሰው እንደዚህ የመሰለ ክስ በእርስዎ ላይ ቢያቀርብ ቢያንስ አቋምዎን ወይም አመለካከትዎን ለመግለጽ አጋጣሚ ቢሰጥዎት በጣም ደስ እንደሚልዎት እርግጠኛ ነኝ፤ አይደለም እንዴ? . . . እንግዲያውስ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አንድ ነገር ባሳይዎትስ . . . ?’

  • ዕድል
    ከቅዱሳን ጽሑፎች እየጠቀሱ ማመራመር
    • ዕድል

      ፍቺ:- መፈጸሙ የማይቀርና ብዙ ጊዜ መጥፎ ውጤት የሚያስከትል ነገር ነው። ማንኛውም ነገር በመለኮታዊ ፈቃድ ወይም ከሰው በላይ በሆነ ኃይል የተወሰነ ነው፤ ማንኛውም ነገር የሚፈጸመው አስቀድሞ በተወሰነው መሠረት ነው የሚል እምነት ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት አይደለም።

      እያንዳንዱ ሰው ‘የሚሞትበት ጊዜ’ አስቀድሞ የተወሰነ ነውን?

      ይህ እምነት በግሪኮችና በሮማውያን ዘንድ በሠፊው ተቀባይነት ያገኘነበር። አረማውያን በነበሩት ግሪካውያን አፈታሪክ መሠረት ዕድል የሕይወትን ክር የምትፈትል፣ ርዝመቱን የምትወስንና የምትቆርጥ የሦስት አማልክት ጥምረት ናት።

      መክብብ 3:1, 2 “ለመሞትም ጊዜ አለው” በማለት ይናገራል። ነገር

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ