መዝሙር 147
የዘላለም ሕይወት ተስፋ ተሰጥቶናል
በወረቀት የሚታተመው
1. የዘላለም ሕይወት ተስፋ
ለሰው ልጆች ተሰጥቷል።
‘ገሮች ምድርን ይወርሳሉ’፤
ተስፋው ይፈጸማል።
(አዝማች)
የዘላለም ሕይወት
ተስፋ ተሰጥቶናል።
በ’ርግጥ ይፈጸማል፤
አምላክ ቃል ገብቷል።
2. ምድር ገነት ትሆናለች፤
ሰውም ፍጹም ይሆናል።
ይሖዋ በምድራችን ላይ
ሰላምን ያሰፍናል።
(አዝማች)
የዘላለም ሕይወት
ተስፋ ተሰጥቶናል።
በ’ርግጥ ይፈጸማል፤
አምላክ ቃል ገብቷል።
3. በቅርብ ሙታን ይነሳሉ፤
ያኔ ሐዘን ይረሳል።
ይሖዋ በርኅራኄው
እንባን ካይን ያብሳል።
(አዝማች)
የዘላለም ሕይወት
ተስፋ ተሰጥቶናል።
በ’ርግጥ ይፈጸማል፤
አምላክ ቃል ገብቷል።