-
ዘፍጥረት 7:11, 12አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
11 ኖኅ በተወለደ በ600ኛው ዓመት፣ በሁለተኛው ወር ከወሩም በ17ኛው ቀን፣ በዚያ ቀን፣ ተንጣሎ የሚገኘው ጥልቅ ውኃ ምንጮች ሁሉ ተነደሉ፤ የሰማያት የውኃ በሮችም ተከፈቱ።+ 12 ዝናቡም ለ40 ቀንና ለ40 ሌሊት በምድር ላይ ወረደ።
-