-
ዘፀአት 20:8አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
8 “የሰንበትን ቀን ቅዱስ አድርገህ መጠበቅ እንዳለብህ አትርሳ።+
-
-
ዘፀአት 20:11አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
11 ምክንያቱም ይሖዋ ሰማያትን፣ ምድርን፣ ባሕርንና በውስጣቸው ያሉትን ነገሮች ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ ሠርቶ ካጠናቀቀ በኋላ በሰባተኛው ቀን ማረፍ ጀምሯል።+ ይሖዋ የሰንበትን ቀን የባረከውና የቀደሰው ለዚህ ነው።
-
-
ዘፀአት 31:13አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
13 “ለእስራኤላውያን እንዲህ ብለህ ንገራቸው፦ ‘እናንተን የምቀድሳችሁ እኔ ይሖዋ መሆኔን እንድታውቁ የሚያደርግ፣ በትውልዶቻችሁ ሁሉ በእኔና በእናንተ መካከል ያለ ምልክት ስለሆነ በተለይ ሰንበቴን ማክበር አለባችሁ።+
-
-
ሉቃስ 6:5አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
5 ከዚያም “የሰው ልጅ የሰንበት ጌታ ነው” አላቸው።+
-