132 ይሖዋ ሆይ፣ ዳዊትን፣
የደረሰበትንም መከራ ሁሉ አስታውስ፤+
2 ለይሖዋ እንዴት እንደማለ፣
ኃያል ለሆነው ለያዕቆብ አምላክ እንዴት እንደተሳለ አስብ፦+
3 “ወደ ድንኳኔ፣ ወደ ቤቴ አልገባም።+
ወደ መኝታዬ፣ ወደ አልጋዬ አልወጣም፤
4 ዓይኖቼ እንዲያንቀላፉ፣
ሽፋሽፍቶቼም እንዲያሸልቡ አልፈቅድም፤
5 ይህም ለይሖዋ ስፍራ፣
ኃያል ለሆነው የያዕቆብ አምላክም ያማረ መኖሪያ እስከማገኝ ድረስ ነው።”+