-
1 ሳሙኤል 27:12አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
12 ስለዚህ አንኩስ ‘በእርግጥም ይህ ሰው በገዛ ሕዝቦቹ በእስራኤላውያን ዘንድ እንደ ጥንብ ተቆጥሯል፤ ስለሆነም ዕድሜ ልኩን አገልጋዬ ይሆናል’ ብሎ ስላሰበ ዳዊትን አመነው።
-
-
1 ሳሙኤል 29:3አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
3 የፍልስጤም መኳንንት ግን “እነዚህ ዕብራውያን እዚህ ምን ያደርጋሉ?” አሉ። በዚህ ጊዜ አንኩስ የፍልስጤምን መኳንንት “ይህ ሰው ከእኔ ጋር ለአንድ ዓመት ወይም ከዚያ በላይ አብሮኝ የኖረው የእስራኤል ንጉሥ የሳኦል አገልጋይ የሆነው ዳዊት ነው።+ ወደ እኔ ከተጠጋበት ቀን አንስቶ እስከዚህች ዕለት ድረስ ምንም ስህተት አላገኘሁበትም” አላቸው።
-