-
2 ነገሥት 7:1, 2አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
7 ኤልሳዕም እንዲህ አለ፦ “የይሖዋን ቃል ስሙ። ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ ‘ነገ በዚህ ሰዓት ገደማ በሰማርያ በር* ላይ አንድ የሲህ መስፈሪያ* የላመ ዱቄት በአንድ ሰቅል* እንዲሁም ሁለት የሲህ መስፈሪያ ገብስ በአንድ ሰቅል ይሸጣል።’”+ 2 በዚህ ጊዜ ንጉሡ የሚተማመንበት የጦር መኮንን የእውነተኛውን አምላክ ሰው “ይሖዋ የሰማይን የውኃ በሮች ቢከፍት እንኳ እንዲህ ያለ ነገር* ሊፈጸም ይችላል?”+ አለው። ኤልሳዕም “ይህን በገዛ ዓይኖችህ ታያለህ፤+ ሆኖም ከዚያ ምንም አትቀምስም”+ አለው።
-