-
2 ሳሙኤል 8:5-8አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
5 የደማስቆዎቹ ሶርያውያን፣+ የጾባህን ንጉሥ ሃዳድኤዜርን ለመርዳት በመጡ ጊዜ ዳዊት ከሶርያውያን መካከል 22,000 ሰዎችን ገደለ።+ 6 ከዚያም ዳዊት በደማስቆ ሶርያ የጦር ሰፈሮች አቋቋመ፤ ሶርያውያንም የዳዊት አገልጋዮች ሆኑ፤ ግብርም ገበሩለት። ይሖዋ ዳዊትን በሄደበት ሁሉ ድል አቀዳጀው።*+ 7 በተጨማሪም ዳዊት ከሃዳድኤዜር አገልጋዮች ላይ ከወርቅ የተሠሩ ክብ ጋሻዎችን ወሰደ፤ ወደ ኢየሩሳሌምም አመጣቸው።+ 8 ደግሞም ንጉሥ ዳዊት የሃዳድኤዜር ከተሞች ከሆኑት ከቤጣህ እና ከበሮታይ እጅግ ብዙ መዳብ ወሰደ።
-