-
1 ነገሥት 8:37-40አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
37 “በምድሪቱ ላይ ረሃብ+ ወይም ቸነፈር፣ የሚለበልብና የሚያደርቅ ነፋስ ወይም ዋግ+ ቢከሰት፣ የአንበጣ መንጋ ወይም የማይጠግብ አንበጣ* ቢመጣ አሊያም ጠላቶቻቸው በምድሪቱ ላይ ባለ በየትኛውም ከተማ* ውስጥ ሳሉ ቢከቧቸው ወይም ደግሞ ማንኛውም ዓይነት መቅሰፍት አሊያም ማንኛውም ዓይነት በሽታ ቢከሰትና+ 38 ማንኛውም ሰው ወይም ሕዝብህ እስራኤል በሙሉ (እያንዳንዱ የልቡን ጭንቀት ያውቃልና)+ ወደ አንተ ለመጸለይ ወይም ሞገስ እንድታሳየው ልመና+ ለማቅረብ እጁን ወደዚህ ቤት ቢዘረጋ 39 አንተ ከመኖሪያ ቦታህ+ ከሰማያት ሆነህ ስማ፤ ደግሞም ይቅር በል፤+ እርምጃም ውሰድ፤ ለእያንዳንዱም እንደ ሥራው ብድራቱን ክፈለው፤+ ምክንያቱም አንተ ልቡን ታውቃለህ (የሰውን ልብ በሚገባ የምታውቀው አንተ ብቻ ነህ)፤+ 40 ይህም ለአባቶቻችን በሰጠኸው ምድር ላይ በሚኖሩበት ዘመን ሁሉ አንተን እንዲፈሩ ነው።
-