የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘዳግም 32:31
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 31 የእነሱ ዓለት እንደ እኛ ዓለት አይደለም፤+

      ጠላቶቻችንም እንኳ ይህን ተረድተዋል።+

  • 1 ሳሙኤል 2:2
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    •  2 እንደ ይሖዋ ያለ ቅዱስ ማንም የለም፣

      ያለአንተ ማንም የለም፤+

      እንደ አምላካችን ያለ ዓለት የለም።+

  • 2 ሳሙኤል 22:32-43
    አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
    • 32 ደግሞስ ከይሖዋ ሌላ አምላክ ማን ነው?+

      ከአምላካችንስ በቀር ዓለት ማን ነው?+

      33 እውነተኛው አምላክ ጠንካራ ምሽጌ ነው፤+

      መንገዴንም ፍጹም ያደርግልኛል።+

      34 እግሮቼን እንደ ዋልያ እግሮች ያደርጋል፤

      በከፍታ ቦታዎች ላይ ያቆመኛል።+

      35 እጆቼን ለጦርነት ያሠለጥናል፤

      ክንዶቼ የመዳብ ደጋን ማጠፍ ይችላሉ።

      36 የመዳን ጋሻህን ትሰጠኛለህ፤

      ትሕትናህም ታላቅ ያደርገኛል።+

      37 ለእርምጃዬ መንገዱን ታሰፋልኛለህ፤

      እግሮቼ* አያዳልጣቸውም።+

      38 ጠላቶቼን አሳድጄ አጠፋቸዋለሁ፤

      ተጠራርገው እስኪጠፉ ድረስ ወደ ኋላ አልመለስም።

      39 እንዳያንሰራሩም ጠራርጌ አጠፋቸዋለሁ፣ አደቃቸዋለሁ፤+

      እግሬ ሥር ይወድቃሉ።

      40 ለውጊያው ብርታት ታስታጥቀኛለህ፤+

      ጠላቶቼ ሥሬ እንዲወድቁ ታደርጋለህ።+

      41 ጠላቶቼ ከእኔ እንዲሸሹ ታደርጋለህ፤*+

      እኔም የሚጠሉኝን አጠፋለሁ።*+

      42 እርዳታ ለማግኘት ይጮኻሉ፤ ሆኖም የሚያድናቸው የለም፤

      ወደ ይሖዋም ይጮኻሉ፤ እሱ ግን አይመልስላቸውም።+

      43 በምድር ላይ እንዳለ አቧራ አደቃቸዋለሁ፤

      በመንገድ ላይ እንዳለ ጭቃ እረግጣቸዋለሁ፤ አደቃቸዋለሁ።

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ