-
2 ሳሙኤል 22:32-43አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
32 ደግሞስ ከይሖዋ ሌላ አምላክ ማን ነው?+
ከአምላካችንስ በቀር ዓለት ማን ነው?+
34 እግሮቼን እንደ ዋልያ እግሮች ያደርጋል፤
በከፍታ ቦታዎች ላይ ያቆመኛል።+
35 እጆቼን ለጦርነት ያሠለጥናል፤
ክንዶቼ የመዳብ ደጋን ማጠፍ ይችላሉ።
36 የመዳን ጋሻህን ትሰጠኛለህ፤
ትሕትናህም ታላቅ ያደርገኛል።+
38 ጠላቶቼን አሳድጄ አጠፋቸዋለሁ፤
ተጠራርገው እስኪጠፉ ድረስ ወደ ኋላ አልመለስም።
39 እንዳያንሰራሩም ጠራርጌ አጠፋቸዋለሁ፣ አደቃቸዋለሁ፤+
እግሬ ሥር ይወድቃሉ።
42 እርዳታ ለማግኘት ይጮኻሉ፤ ሆኖም የሚያድናቸው የለም፤
ወደ ይሖዋም ይጮኻሉ፤ እሱ ግን አይመልስላቸውም።+
43 በምድር ላይ እንዳለ አቧራ አደቃቸዋለሁ፤
በመንገድ ላይ እንዳለ ጭቃ እረግጣቸዋለሁ፤ አደቃቸዋለሁ።
-