8 ኤፍሬም ሆይ፣ እንዴት ልተውህ እችላለሁ?+
እስራኤል ሆይ፣ እንዴት አሳልፌ ልሰጥህ እችላለሁ?
እንዴትስ እንደ አድማህ አደርግሃለሁ?
ደግሞስ እንዴት እንደ ጸቦይም ላደርግህ እችላለሁ?+
ስለ አንተ ያለኝ አመለካከት ተለወጠ፤
የርኅራኄ ስሜቴም ተቀሰቀሰ።+
9 የሚነድ ቁጣዬን አልገልጽም።
ኤፍሬምን ዳግመኛ አላጠፋም፤+
እኔ አምላክ እንጂ ሰው አይደለሁምና፤
በመካከልህ ያለሁ ቅዱስ አምላክ ነኝ፤
በአንተም ላይ በቁጣ አልመጣም።