-
ኤርምያስ 31:35-37አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
-
-
35 ስሙ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ የሆነው፣
በቀን እንድታበራ ፀሐይን የሰጠው፣
በሌሊትም እንዲያበሩ የጨረቃንና የከዋክብትን ሕጎች ያወጣው፣*
ባሕሩን የሚያናውጠውና ኃይለኛ ማዕበል የሚያስነሳው
ይሖዋ እንዲህ ይላል፦+
36 “‘የእስራኤል ዘር ምንጊዜም በፊቴ የሚኖር ብሔር መሆኑ የሚያከትመው’ ይላል ይሖዋ፣
‘ይህ ሥርዓት ከተሻረ ብቻ ነው።’”+
37 ይሖዋ እንዲህ ይላል፦ “‘መላውን የእስራኤል ዘር፣ በሠሩት ነገር ሁሉ የተነሳ ልተዋቸው የምችለው፣ በላይ ያሉትን ሰማያት መለካት፣ በታች ያሉትንም የምድር መሠረቶች መመርመር የሚቻል ከሆነ ብቻ ነው’ ይላል ይሖዋ።”+
-