አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ ሚልክያስ የመጽሐፉ ይዘት ሚልክያስ የመጽሐፉ ይዘት 1 ይሖዋ ለሕዝቡ ያለው ፍቅር (1-5) እንከን ያለበት መሥዋዕት ያቀረቡ ካህናት (6-14) የአምላክ ስም በብሔራት መካከል ታላቅ ይሆናል (11) 2 ካህናቱ ሕዝቡን ሳያስተምሩ ቀሩ (1-9) ካህኑ “በከንፈሮቹ ላይ እውቀት ሊኖረው ይገባል” (7) ሚስቶቻቸውን በመፍታት በደል ፈጸሙ (10-17) “እኔ ፍቺን እጠላለሁ” ይላል ይሖዋ (16) 3 እውነተኛው ጌታ ቤተ መቅደሱን ለማንጻት ይመጣል (1-5) የቃል ኪዳኑ መልእክተኛ (1) ወደ ይሖዋ እንዲመለሱ ማበረታታት (6-12) ይሖዋ አይለወጥም (6) “ወደ እኔ ተመለሱ፤ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ” (7) ‘አሥራቱን ሁሉ አስገቡ፤ ይሖዋም የተትረፈረፈ በረከት ያፈስላችኋል’ (10) ጻድቁ ሰውና ክፉው ሰው (13-18) በአምላክ ፊት የመታሰቢያ መጽሐፍ ተጻፈ (16) በጻድቁና በክፉው መካከል ያለው ልዩነት (18) 4 ከይሖዋ ቀን በፊት ኤልያስ ይመጣል (1-6) ‘የጽድቅ ፀሐይ ትወጣለች’ (2)