የግርጌ ማስታወሻ
e በዘመናዊው የአይሁዳውያን የቀን መቁጠሪያ መሠረት የኒሳን ወር መጀመሩ የሚረጋገጠው በከዋክብት ጥናት አዲስ ጨረቃ ስትታይ ነው፤ ሆኖም በመጀመሪያው መቶ ዘመን ይሠራበት የነበረው ዘዴ ይህ አልነበረም። ከዚህ ይልቅ ወሩ የሚጀምረው በኢየሩሳሌም አዲስ ጨረቃ ስትታይ ነው፤ ይህም በከዋክብት ጥናት መሠረት አዲስ ጨረቃ ወጥታለች ከሚባልበት ዕለት በአንድ ወይም ከዚያ በላይ ቀን ሊዘገይ ይችላል። በዚህ ምክንያት የይሖዋ ምሥክሮች የክርስቶስን ሞት መታሰቢያ በዓል የሚያከብሩበት ቀንና በዘመናችን ያሉ አይሁዳውያን የፋሲካን በዓል የሚያከብሩበት ቀን ሊለያይ የሚችልበት አንዱ ምክንያት ይህ ነው።