የግርጌ ማስታወሻ
a በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ “ቤዛ” ተብለው የተተረጎሙት የዕብራይስጥና የግሪክኛ ቃላት የተከፈለን ክፍያ ወይም ዋጋ ያመለክታሉ። ለምሳሌ ካፋር የሚለው የዕብራይስጥ ቃል “መሸፈን” የሚል ትርጉም አለው፤ ይህ ቃል በዘፍጥረት 6:14 ላይ መርከቡ በቅጥራን እንደተሸፈነ ወይም እንደተለቀለቀ ለመግለጽ ተሠርቶበታል። አብዛኛውን ጊዜ ይህ ቃል ኃጢአትን መሸፈንን የሚያመለክት ነው። (መዝሙር 78:38፣ የግርጌ ማስታወሻ) ከዚህ ጋር ተያያዥነት ያለው ኮፌር የሚለው ቃል አንድን ነገር ለመሸፈን ወይም ለመዋጀት የሚደረገውን ክፍያ ያመለክታል። (ዘፀአት 21:30) በተጨማሪም አብዛኛውን ጊዜ “ቤዛ” ተብሎ የሚተረጎመው ሊትሮን የሚለው የግሪክኛ ቃል “ለመዋጀት የሚከፈል ዋጋ” ተብሎም ሊተረጎም ይችላል። (ማቴዎስ 20:28፣ በሪቻርድ ፍራንሲስ ዌይማውዝ የተዘጋጀው ዘ ኒው ቴስታመንት ኢን ሞደርን ስፒች) የግሪክ ጸሐፊዎች ይህን አገላለጽ አንድን ምርኮኛ ወይም ባሪያ ነፃ ለማውጣት የሚከፈልን ዋጋ ለማመልከት ተጠቅመውበታል።