የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
ማስታወቂያ
አዲስ የገባ ቋንቋ፦ Romany (Meçkar)
  • ዛሬ

ሐሙስ፣ ነሐሴ 28

ይሖዋ ለሚጠሩት ሁሉ፣ በእውነት ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው።—መዝ. 145:18

‘የፍቅር አምላክ’ የሆነው ይሖዋ ከእኛ ጋር ነው! (2 ቆሮ. 13:11) በግለሰብ ደረጃ ትኩረት ይሰጠናል። ‘ታማኝ ፍቅሩ እንደከበበን’ እርግጠኞች ነን። (መዝ. 32:10) ይሖዋ ፍቅሩን ያሳየን እንዴት እንደሆነ ይበልጥ ባሰላሰልን መጠን እሱ ይበልጥ እውን ይሆንልናል፤ እንዲሁም ይበልጥ ወደ እሱ እንቀርባለን። በነፃነት ልናነጋግረውና ፍቅሩ ምን ያህል እንደሚያስፈልገን ልንነግረው እንችላለን። ይሖዋ ስሜታችንን እንደሚረዳልንና ሊረዳን እንደሚጓጓ በመተማመን የሚያሳስበንን ነገር ሁሉ ልናካፍለው እንችላለን። (መዝ. 145:19) ብርድ በሆነ ቀን የተቀጣጠለ እሳት እንደሚስበን ሁሉ የይሖዋ ፍቅርም ወደ እሱ እንድንቀርብ ያነሳሳናል። የይሖዋ ፍቅር ታላቅና ማራኪ ነው። እንግዲያው የይሖዋን ፍቅር አጣጥም። ሁላችንም ‘ይሖዋን እወደዋለሁ’ በማለት ለፍቅሩ ምላሽ እንስጥ!—መዝ. 116:1፤ w24.01 31 አን. 19-20

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ዓርብ፣ ነሐሴ 29

ስምህን አሳውቄአቸዋለሁ።—ዮሐ. 17:26

ኢየሱስ ለሰዎች የአምላክ ስም ይሖዋ መሆኑን ከማሳወቅ ያለፈ ነገር አድርጓል። ኢየሱስ ያስተማራቸው አይሁዳውያን ቀድሞውንም የአምላክን ስም ያውቃሉ። ሆኖም ኢየሱስ ግንባር ቀደም ሆኖ ስለ እሱ ‘ገልጿል።’ (ዮሐ. 1:17, 18) ለምሳሌ የዕብራይስጥ ቅዱሳን መጻሕፍት ይሖዋ መሐሪና ሩኅሩኅ እንደሆነ ይናገራሉ። (ዘፀ. 34:5-7) ኢየሱስ ስለ አባካኙ ልጅና ስለ አባቱ የሚገልጸውን ምሳሌ በተናገረበት ወቅት ይህንን እውነት ይበልጥ ግልጽ አድርጎታል። አባትየው ንስሐ የገባውን ልጁን ‘ገና ሩቅ ሳለ እንዳየው፣’ ሮጦ ሄዶ እንደተቀበለው፣ እንዳቀፈው እንዲሁም በሙሉ ልቡ ይቅር እንዳለው ስናነብ የይሖዋ ምሕረትና ርኅራኄ ግልጽ ሆኖ ይታየናል። (ሉቃስ 15:11-32) በእርግጥም ኢየሱስ የአባቱን እውነተኛ ማንነት ገልጦልናል። w24.02 10 አን. 8-9

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ቅዳሜ፣ ነሐሴ 30

ከአምላክ በምናገኘው መጽናኛ [ሰዎችን እናጽናና]።—2 ቆሮ. 1:4

ይሖዋ የተጨነቁ ሰዎችን ያጽናናል። ለሌሎች በመራራትና እነሱን በማጽናናት ይሖዋን መምሰል የምንችለው እንዴት ነው? ይህን ማድረግ የምንችልበት አንዱ መንገድ ማጽናኛ ለመስጠት የሚያነሳሱ ባሕርያትን በልባችን ውስጥ በማዳበር ነው። ከእነዚህ ባሕርያት መካከል አንዳንዶቹ የትኞቹ ናቸው? ‘ሁልጊዜ እርስ በርስ ለመጽናናት’ የሚያነሳሳ ፍቅር እንዲኖረን ምን ይረዳናል? (1 ተሰ. 4:18) የሌላውን ስሜት መረዳት እንዲሁም የወንድማማች መዋደድንና ደግነትን የመሳሰሉ ባሕርያትን ማዳበር ይኖርብናል። (ቆላ. 3:12፤ 1 ጴጥ. 3:8) እነዚህ ባሕርያት የሚረዱን እንዴት ነው? ርኅራኄ እና ተመሳሳይ ባሕርያት የማንነታችን ክፍል ከሆኑ የተጨነቁ ሰዎችን እንድናጽናና ውስጣችን ይገፋፋናል። ኢየሱስ እንዳለው “አንደበት የሚናገረው በልብ ውስጥ የሞላውን ነውና። ጥሩ ሰው በልቡ ካከማቸው መልካም ነገር ጥሩ ነገር ያወጣል።” (ማቴ. 12:34, 35) በእርግጥም እርዳታ የሚያስፈልጋቸውን ወንድሞቻችንን እና እህቶቻችንን ማጽናናት ለእነሱ ያለንን ፍቅር የምንገልጽበት ወሳኝ መንገድ ነው። w23.11 10 አን. 10-11

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ