የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ሰኞ፣ መስከረም 1

እንደ ንጋት ፀሐይ የሚያበራ ብርሃን ከላይ ይወጣልናል።—ሉቃስ 1:78

አምላክ ለኢየሱስ የሰው ልጆችን ችግሮች በሙሉ ለመፍታት የሚያስችል ኃይል ሰጥቶታል። ኢየሱስ የፈጸማቸው ተአምራት በራሳችን ፈጽሞ ልናሸንፋቸው የማንችላቸውን ችግሮች የመቅረፍ ኃይል እንዳለው ያሳያሉ። ለምሳሌ የሰው ልጆች ለሚያጋጥሟቸው ችግሮች ዋነኛ መንስኤ የሆነውን በዘር የወረስነውን ኃጢአት እንዲሁም የኃጢአት ውጤት የሆኑትን በሽታንና ሞትን ለማስወገድ የሚያስችል ኃይል አለው። (ማቴ. 9:1-6፤ ሮም 5:12, 18, 19) “ማንኛውንም ዓይነት” በሽታ የመፈወስ፣ አልፎ ተርፎም ሙታንን የማስነሳት ኃይል እንዳለው የፈጸማቸው ተአምራት ያሳያሉ። (ማቴ. 4:23፤ ዮሐ. 11:43, 44) በተጨማሪም ኃይለኛ ማዕበልን ጸጥ የማሰኘት እንዲሁም ክፉ መናፍስትን የማስወጣት ችሎታ አለው። (ማር. 4:37-39፤ ሉቃስ 8:2) ይሖዋ ለልጁ እንዲህ ያለ ኃይል እንደሰጠው ማወቅ በእርግጥም የሚያጽናና ነው። የአምላክ መንግሥት ስለሚያመጣቸው በረከቶች የሚናገሩት ተስፋዎች በሙሉ እንደሚፈጸሙ እርግጠኞች መሆን እንችላለን። ኢየሱስ ምድር ላይ በነበረበት ወቅት የፈጸማቸው ተአምራት በሰማይ የአምላክ መንግሥት ንጉሥ ሆኖ በስፋት ስለሚያከናውነው ሥራ ያስተምሩናል። w23.04 3 አን. 5-7

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ማክሰኞ፣ መስከረም 2

መንፈስ ሁሉንም ነገሮች አልፎ ተርፎም የአምላክን ጥልቅ ነገሮች ይመረምራል።—1 ቆሮ. 2:10

ጉባኤያችሁ ብዙ አስፋፊዎች ካሉትና ብዙ ጊዜ የመመለስ ዕድል የማታገኙ ከሆነ ተስፋ ልትቆርጡ ትችላላችሁ። ሆኖም መልስ ለመመለስ መሞከራችሁን አታቁሙ። ለእያንዳንዱ ስብሰባ በርከት ያሉ መልሶችን ተዘጋጁ። እንዲህ ካደረጋችሁ በስብሰባው መጀመሪያ አካባቢ ሐሳብ የመስጠት ዕድል ባታገኙም እንኳ ስብሰባው ሲቀጥል አጋጣሚ ልታገኙ ትችላላችሁ። ለመጠበቂያ ግንብ ጥናት ስትዘጋጁ እያንዳንዱ አንቀጽ ከዋናው ጭብጥ ጋር የሚያያዘው እንዴት እንደሆነ ለማሰብ ሞክሩ። እንዲህ ካደረጋችሁ በተለያዩ አንቀጾች ላይ የምትሰጡት ሐሳብ መኖሩ አይቀርም። በተጨማሪም ለማስረዳት የሚከብዱ ጥልቅ እውነቶችን በያዙ አንቀጾች ላይ ሐሳብ ለመስጠት ልትዘጋጁ ትችላላችሁ። ለምን? ምክንያቱም እንዲህ ባሉ አንቀጾች ላይ እጃቸውን የሚያወጡት ሰዎች ቁጥር ያን ያህል ብዙ ላይሆን ይችላል። ይሁንና ሐሳብ የመስጠት ዕድል ሳታገኙ የተወሰኑ ስብሰባዎች ቢያልፉስ? ከስብሰባው በፊት ወደ መሪው ሄዳችሁ በመረጣችሁት አንቀጽ ላይ ሐሳብ የመስጠት ዕድል እንዲሰጣችሁ ጠይቁት። w23.04 21-22 አን. 9-10

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ረቡዕ፣ መስከረም 3

ዮሴፍ . . . የይሖዋ መልአክ ባዘዘው . . . መሠረት ሚስቱን ወደ ቤቱ ወሰዳት።—ማቴ. 1:24

ዮሴፍ የይሖዋን መመሪያ ለመከተል ፈቃደኛ ነበር፤ ይህም ጥሩ ባል እንዲሆን ረድቶታል። አምላክ ቢያንስ ሦስት ጊዜ ለዮሴፍ ቤተሰቡን የሚነካ መመሪያ ሰጥቶታል። ትልቅ ለውጥ ማድረግ ቢጠይቅበትም እንኳ በሦስቱም ጊዜያት የይሖዋን መመሪያ ወዲያውኑ ታዟል። (ማቴ. 1:20፤ 2:13-15, 19-21) ዮሴፍ የአምላክን መመሪያ በመከተል ማርያምን ከጉዳት ጠብቋታል፣ ደግፏታል እንዲሁም የሚያስፈልጋትን ነገር አሟልቶላታል። ዮሴፍ ያደረገው ነገር ማርያም ለእሱ ያላትን ፍቅርና አክብሮት ምንኛ አጠናክሮት ይሆን! ባሎች፣ ቤተሰቦቻችሁን ከምትንከባከቡበት መንገድ ጋር በተያያዘ የመጽሐፍ ቅዱስን መመሪያ በመፈለግ የዮሴፍን ምሳሌ መከተል ትችላላችሁ። ለውጥ ማድረግ ቢጠይቅባችሁም እንኳ የመጽሐፍ ቅዱስን ምክር የምትከተሉ ከሆነ ለሚስቶቻችሁ ያላችሁን ፍቅር ታሳያላችሁ፤ ትዳራችሁንም ታጠናክራላችሁ። በትዳር ዓለም ከ20 ዓመት በላይ ያሳለፈች በቫኑዋቱ የምትኖር እህት እንዲህ ብላለች፦ “ባለቤቴ የይሖዋን መመሪያ ለማግኘት ጥረት ሲያደርግና መመሪያውን በሥራ ላይ ሲያውል ለእሱ ያለኝ አክብሮት ይጨምራል። እተማመንበታለሁ፤ እንዲሁም ጥሩ ውሳኔ እንደሚያደርግ እርግጠኛ ነኝ።” w23.05 21 አን. 5

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ