የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • th ጥናት 20 ገጽ 23
  • ግቡን የሚመታ መደምደሚያ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ግቡን የሚመታ መደምደሚያ
  • ለማንበብ እና ለማስተማር የተቻለህን ሁሉ ጥረት አድርግ
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ግቡን የሚመታ መደምደሚያ
    በቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት ከሚሰጠው ሥልጠና ተጠቀም
  • የጥቅሱን ዓላማ ግልጽ ማድረግ
    ለማንበብ እና ለማስተማር የተቻለህን ሁሉ ጥረት አድርግ
  • የአድማጮችን ልብ ለመንካት መጣር
    ለማንበብ እና ለማስተማር የተቻለህን ሁሉ ጥረት አድርግ
  • የትምህርቱን ጥቅም ግልጽ ማድረግ
    ለማንበብ እና ለማስተማር የተቻለህን ሁሉ ጥረት አድርግ
ለተጨማሪ መረጃ
ለማንበብ እና ለማስተማር የተቻለህን ሁሉ ጥረት አድርግ
th ጥናት 20 ገጽ 23

ጥናት 20

ግቡን የሚመታ መደምደሚያ

ጥቅስ

መክብብ 12:13, 14

ፍሬ ሐሳብ፦ መደምደሚያህ፣ አድማጮችህ ትምህርቱን አምነው እንዲቀበሉና እርምጃ እንዲወስዱ የሚያነሳሳ መሆን ይኖርበታል።

ይህን ማድረግ የምትችለው እንዴት ነው?

  • መደምደሚያህ ካነሳኸው ርዕሰ ጉዳይ ጋር በቀጥታ የሚያያዝ መሆን ይኖርበታል። ስታብራራቸው የነበሩትን ዋና ዋና ነጥቦችና ጭብጡን ደግመህ መናገር አሊያም በሌላ አባባል መጥቀስ ትችላለህ።

  • አድማጮችህን ለተግባር አነሳሳቸው። አድማጮችህ ሊወስዱት የሚገባው እርምጃ ምን እንደሆነ እንዲሁም ይህን ማድረግ ያለባቸው ለምን እንደሆነ ግለጽ። ትምህርቱ አስፈላጊ እንደሆነ እንዲሁም የምትናገረውን ነገር ከልብህ እንደምታምንበት በሚያሳይ መንገድ ተናገር።

  • መደምደሚያህ አጭርና ያልተወሳሰበ ይሁን። አዳዲስ ዋና ዋና ነጥቦችን አታንሳ። በተቻለህ መጠን ጥቂት ቃላት ተጠቅመህ አድማጮችህን ለተግባር አነሳሳቸው።

    ጠቃሚ ሐሳብ

    ንግግርህን የምትደመድመው በጥድፊያ መሆን የለበትም፤ የድምፅህ መጠንም እየቀነሰ መሄድ አይኖርበትም። መጨረሻ ላይ የምትናገራቸው ዓረፍተ ነገሮች ንግግርህን እየደመደምክ እንዳለህ የሚጠቁሙ መሆን አለባቸው።

ለአገልግሎት

ውይይቱን ስትደመድም፣ የምታነጋግረው ሰው እንዲያስታውስ የምትፈልገውን ዋና ነጥብ ደግመህ ተናገር። ውይይታችሁ በድንገት ቢቋረጥ እንኳ ከግለሰቡ ጋር በጥሩ ሁኔታ ለመለያየት ጥረት አድርግ። ግለሰቡ ቢያመናጭቅህ እንኳ ሌላ ጊዜ መልእክቱን ለመስማት ሊያነሳሳው የሚችል ምላሽ መስጠትህ ጠቃሚ ነው።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ